ጋርዲዮላ በዌምብሊ እንዳደረጉት በኢቲሃድ ስታዲየም ቢጫወቱ እንደገና ያሸንፉ እንደሆነ ተጠይቆ ሲመልስ “ለ95 ደቂቃዎች እንደተጫወትነው ከተጫወትንና እነሱም ያደረጉትን ካደረጉ እናሸንፋለን” ብሏል። አክሎም “ነገር ግን እግር ኳስ የማይገመት ስፖርት ነው። ሚኬልን ጥቂት አውቀዋለሁ፣ የሆነ ነገር ማስተካከላቸው አይቀርም፤ እኛም ለዛ መዘጋጀት አለብን። በመጨረሻ ግን ነገሩ ቀላል ነው፤ ተጫዋቾች በግል የሚያሳዩት ብቃት ይወስነዋል” ሲል ገልጿል።
በካራባኦ ካፕ ፍጻሜ ያገኙት ድል ትልቅ የስነ-ልቦና ጥንካሬ ሊሰጣቸው እንደሚችል ቢታሰብም፣ ጋርዲዮላ ግን “አዎ፣ ነገር ግን በተመሳሳይ ተሸንፈን ቢሆን ኖሮ የበለጠ እንድንጠነክር ማስጠንቀቂያ ይሆነን ነበር” ብሏል። “ጨዋታውን በምን አይነት መንገድ እንደምንጀምረው አላውቅም። የካራባኦ ካፕ አስፈላጊ ነው፣ ነገር ግን የፕሪሚየር ሊግ ዋጋው እጅግ የላቀ ነው” ሲል አፅንዖት ሰጥቷል።
አርሰናል እሁድ እለት ድል የሚያቀና ከሆነ ከጋርዲዮላ ቡድን በአንድ ጨዋታ በልጦ 33 ጨዋታዎችን በማድረግ በዘጠኝ ነጥብ ልዩነት መሪነቱን ያጠናክራል። የሰሜን ለንደኑ ክለብ ለመጨረሻ ጊዜ የሊጉ ሻምፒዮን የሆነው እ.ኤ.አ. በ2004 ሲሆን፣ የሲቲው አሰልጣኝ ይህ ለተጋጣሚያቸው ተጨማሪ መነሳሳትን እንደሚሰጥ ያምናሉ። ጋርዲዮላ ሲቀጥልም “ለ22 ዓመታት ዋንጫ አለማንሳት፤ ካሸነፉ ሁሉም ነገር እንደሚያበቃ ማወቃቸው ብልጫ ይሰጣቸው ይሆን? እዚህ ጋር ትልቅ የስነ-ልቦና ጉዳይ አለ። ላላቸው ብቃት ትልቅ ክብር አለን፤ ነገር ግን እኔ ሁልጊዜ ትኩረት የማደርገው በታክቲክ እና በስነ-ልቦና እኛ ምን ማድረግ እንዳለብን ላይ ነው” ብሏል።
አርሰናል በሚከተለው ጥንቃቄ የተሞላበት አጨዋወት ትችቶች ቢሰነዘሩበትም፣ ጋርዲዮላ ግን ቡድኑን መመልከት እንደሚያስደስተው ተናግሯል። “አዎ፣ ሰዎች በጣም ጠያቂ ናቸው፤ ሚዲያውም ሆነ ደጋፊው” ያለው ጋርዲዮላ “እነሱን መመልከት ያስደስተኛል፣ ብዙ ነገሮችንም እማራለሁ። ሰዎች የሚፈልጉት ማሸነፍን ነው። ለ22 ዓመታት የፕሪሚየር ሊጉን ዋጋ አለማግኘት ልዩ የሆነ ረሃብ ይፈጥራል፤ ያ ደግሞ እኛ ልንታገለው የማንችለው ነገር ነው። እኛ ትኩረት ማድረግ ያለብን በራሳችን አጨዋወት ላይ ብቻ ነው” ሲል ገልጿል። ስለ ሲቲ የተጫዋቾች ዜና ሲናገርም ሩበን ዲያስ አሁንም በጉዳት ላይ ሲሆን ኦሬሊ ግን ለጨዋታው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል።