በዩናይትድ ስቴትስ ከሴኔጋል፣ ኢራቅ እና ኖርዌይ ጋር የምድብ ጨዋታዎችን የሚያደርጉት ዴሻምፕስ፥ “ሁጎ ማክሰኞ ምሽት ከፒኤስጂ ጋር በነበረው ጨዋታ ከባድ ጉዳት ደርሶበታል” ብለዋል። አሰልጣኙ አክለውም “እንደ አለመታደል ሆኖ የጉዳቱ ክብደት ከሊቨርፑል ጋር የውድድር ዘመኑን እንዳያጠናቅቅ እና በዓለም ዋንጫው ላይ እንዳይሳተፍ ያደርገዋል” ሲሉ ገልጸዋል። ኤኪቲኬ በዚህ የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 17 ግቦችን በማስቆጠር የሊቨርፑል ቀዳሚ ግብ አግቢ ሲሆን፥ የእሱ አለመኖር የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ለማረጋገጥ ስድስት ጨዋታዎች ለቀሩት አርኔ ስሎት ሌላ ከባድ መታ መታ ነው።
አጥቂው ባለፈው ክረምት ከኢንትራክት ፍራንክፈርት በ79 ሚሊዮን ፓውንድ ሊደርስ በሚችል የዝውውር ውል የተፈረመ ሲሆን፥ የሊቨርፑል ውድ የዝውውር እንቅስቃሴ ዋነኛ አካል ሆኖ ቆይቷል። ከኤኪቲኬ የቀድሞ ክለብ ፒኤስጂ ጋር የተደረገው የመልስ ጨዋታ አጥቂው፣ አሌክሳንደር ኢሳክ እና ፍሎሪያን ዊርትዝ ለሊቨርፑል በአንድነት ጨዋታ የጀመሩበት ለሁለተኛ ጊዜ ብቻ ሲሆን በአንፊልድ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። በድምሩ 320 ሚሊዮን ፓውንድ የወጣባቸው እነዚህ ሶስት ተጫዋቾች በዚህ የውድድር ዘመን አብረው ሜዳ ላይ የቆዩት ለ115 ደቂቃዎች ብቻ ነው። የኤኪቲኬ አለመገኘት በእግር እና የቁርጭምጭሚት ስብራት ምክንያት ለአራት ወራት ከሜዳ ርቆ የነበረው ኢሳክ በፍጥነት ወደ ብቃቱ የመመለሱን አስፈላጊነት ይጨምራል። መሀመድ ሳላህ በዚህ ክረምት ክለቡን የሚለቅ በመሆኑ፥ የኤኪቲኬ የረጅም ጊዜ ጉዳት በሊቨርፑል የቀጣይ የውድድር ዘመን እቅድ ላይም የራሱ የሆነ ተፅዕኖ ይኖረዋል።