ሃሪ ማጓየር በማንቸስተር ዩናይትድ እስከ 2027 ድረስ የሚቆይ የውል ማራዘሚያ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ ውሉ ለተጨማሪ አንድ ዓመት የማራዘም አማራጭንም አካቷል። ተከላካዩ እ.ኤ.አ በ2019 ከሌስተር ሲቲ ክለቡን የተቀላቀለ ሲሆን፣ የነበረው ውልም በዚህ ክረምት ሊጠናቀቅ ተቃርቦ ነበር።
ማጓየር ስለ ውል ማራዘሙ ሲናገር “ማንቸስተር ዩናይትድን መወከል ትልቅ ክብር ነው። ይህ እኔን እና ቤተሰቤን በየቀኑ የሚያኮራ ኃላፊነት ነው። በዚህ አስደናቂ ክለብ ውስጥ ቆይታዬን ቢያንስ ለስምንት የውድድር ዘመናት ለማራዘም በመቻሌ እና በልዩ ደጋፊዎቻችን ፊት በመጫወት ተጨማሪ አስደናቂ ትዝታዎችን አብረን መፍጠር በመቀጠላችን ደስተኛ ነኝ” ብሏል።
“የዚህን አስደሳች ቡድን ፍላጎት እና አቅም መረዳት ትችላላችሁ። መላው ክለቡ ለዋና ዋና ዋንጫዎች ለመታገል ያለው ቁርጠኝነት ለሁሉም ግልጽ ነው፤ ምርጥ ጊዜያቶቻችን ገና ከፊታችን እንደሚጠብቁን ሙሉ እምነት አለኝ” ሲልም አክሏል። • ተጨማሪ ዝርዝሮች በቅርቡ ይቀርባሉ