አርቴታ ስለ ዎልቭሱ ጨዋታ ሲናገር “ከዎልቭስ ጨዋታ በኋላ ነገሮች ከባድ ነበሩ፤ ነገር ግን የእግር ኳስ ውበት ይሄው ነው” ብሏል። “ጨዋታውን ደግመህ ስትመለከተው እንዴት ያንን ጨዋታ አቻ እንደወጣን ሊገባህ አይችልም። በራስህ ትናደዳለህ፣ ታዝናለህ፣ ታፍራለህም። ሁላችንም ከተለያዩ ሀገራት የመጣን የተለያየ ሰዎች ብንሆንም፣ እንዴት በጋራ ሆነን ‘ይህንን አጋጣሚ እንዴት ወደ መቀየሪያ ነጥብ እንለውጠዋለን? እንዴትስ የተሻልን እንሆናለን?’ ብለን ስንጠይቅ ማየት ደስታን ይሰጣል። ይህ ከስራ በላይ ነው – ፍላጎታችን እና ዓላማችን ነው። በጣም ህመም አለው ነገር ግን ውጤቱ አርኪ ሊሆን ይችላል።”
የአርሰናሉ አሰልጣኝ ላለፉት ሁለት ወራት ያለ አጋማሽ ጨዋታ የሚያሳልፉትን የመጀመሪያ ሳምንት ሲጠባበቁ በከፍተኛ መረጋጋት ውስጥ ነበሩ። “ከምን እንደተሰራን ያሳየን ይመስለኛል፤ ነገር ግን ይህንን ደግመን ደጋግመን ማሳየት አለብን” ብሏል። “እዚያ ሜዳ ላይ ካየሁት ነገር በተለይም ባለፉት 72 ሰዓታት ውስጥ ካሳለፍነው ሁኔታ አንጻር ከዚህ በላይ ልኮራ እና ደስተኛ ልሆን አልችልም።” አርቴታ በተለይ በኤምሬትስ ስታዲየም በነበረው ደርቢ ሶስት ጎሎችን ካስቆጠረ በኋላ አሁን ደግሞ ሁለት ተጨማሪ ጎሎችን ላከለው ኤቤሬቺ ኢዜ ልዩ አድናቆት ሰጥቷል። “አንድ ነገር ለማረጋገጥ እንደሚፈልግ አይ ነበር፤ በዎልቭሱ ጨዋታ ከመጀመሪያው ስላላሰለፍኩት በእኔ ላይ እንኳ ተከፍቶ ነበር” ሲል ተናግሯል።
የቶተንሃሙ አዲስ አሰልጣኝ ኢጎር ቱዶር ከፊታቸው ስላለው ፈተና መጠን ምንም አልደበቁም። “በጣም አዝኛለሁ” ያሉት አሰልጣኙ፣ “ነገር ግን ያለንበትን ደረጃ ለመረዳት እና እውነታውን የሚያሳየን ጨዋታ በማግኘታችን በአንድ በኩል ጥሩ ነው። እያንዳንዳችን በመስታወት ውስጥ ራሳችንን አይተን ልማዶቻችንን መቀየር መጀመር አለብን። ጠንክሮ መስራት ብቸኛው መንገድ ነው” ብለዋል። ቱዶር ስለ “አስተሳሰብ እና የአእምሮ ንቃት” ለውጥ አስፈላጊነት ቢናገሩም፣ ስፐርስ እና አርሰናል በአሁኑ ወቅት “በተለያዩ ዓለማት” ውስጥ እንደሚገኙ አምነዋል። “በአሁኑ ወቅት በዚህ ደረጃ ላይ ያለ ቡድን የማይቀጣህባቸው ብዙ ችግሮች አሉብን። ወደ ላይ ተጭነን መጫወት እንፈልጋለን ነገር ግን ካልተንቀሳቀስክ ትረፍዳለህ። ኳሱን ለመቀማት ፈልገን ነበር ነገር ግን አልቻልንም። ጠንክረን ሄደን ኳሱን ለመውሰድ በአካላዊ ብቃት ዝግጁ መሆን አለብን። ኳሱ በእጃችን እያለ እንኳን በቡድኑ ውስጥ ያለው በራስ የመተማመን እጥረት በግልጽ ይታያል” ብለዋል።
ስፐርስ በአስተሳሰብም ሆነ በአካላዊ ብቃት ጠንካራ እንዳልሆኑ ቢጠቁሙም፣ ቱዶር ተስፋ እንዳልቆረጡ አጽንኦት ሰጥተዋል። “ፍላጎቱን አይቻለሁ፤ ተነሳሽነቱን አይቻለሁ። አልተቆጣሁም ምክንያቱም ያዘጋጀነውን ሁሉ ለማድረግ ፈልገው ነበር ነገር ግን አልቻሉም” ብለዋል። ነገሮችን ለማስተካከል ጊዜ አለ ወይ? ተብለው ሲጠየቁም “በእርግጥ አለ” ሲሉ መልሰዋል።